ዓርብ 21 ኖቬምበር 2014

የማይረሳ ለሊት(ዘጸ12፡42)




 በዚህ ዕለት የሚከበረው በዓል እስራኤል ዘስጋ ለ430 ዓመት በግብጽ ከኖሩ በኋላ በዛሬ ዕለት የወጡበት በዓል ይታሰባል፡፡እስራኤላውያን ወደ ግብጽ ከከነዓን ወጥተው የገቡት
በርሀብ ምክንያት ሲሆን ወንድማቸው ዮሴፍንም አስቀድመው ሸጠውት ነበር፡፡

ከከነዓን ተሰደው በረሀብ ምክንያት ወደ ግብስ 70 ቤተሰብ ሆነውገቡ፡፡ከብዙ ዘመን በ|ላ ዮሴፍን የማያውቅ ፈርዖን ተነሳ፡፡እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላት ቢነሳብን ተደርበው ያጠፉናል
ብሎ መከራና አገዛዘ አጸኑባቸው መከራ እየተቀበሉ ሲሰቃዩ ኖሩ ወንድ ልጆች ሲወለዱ በአዋላጆቻቸው እንዲገደሉ ትዕዛዝ ተሰጠ ራሔል የምትባል ዕብራዊት ባሏ ሮቤል ሞቶባት የባሏን ሥራ
ደርበሽ ሥሪ ተብላ ጭቃ ስትረግጥ ምጥ ያዛት ጥቂት ልረፍ አለች የሚሰራው ግብጻዊ እርገጪ ብሎ አስገደዳት በማህፀኗ የነበሩት መንታ ሕፃናት ከእግሮ ስር ወደቁ የልጅ ደም ግንብ ያጠነክራል
ብሎ ከጭቃው ጋር እርገጫቸው አላት እንባዋን ወደ ሰማይ ረጨች #ቃል ተሰማዐ በራማ ወሰቆቃው ወገዓር ራሄል እንዘ ትበኪ በእንተ ውሉዳ ወአበየት ተናዝዞ ወነጊፈ ለህ; (ኤር 31፡15፤ማቴ 2፡17)

ከዚህ በ|ላ እግዚአብሔር ለሙሴ ፈርዖንን ሕዝቤን ልቀቅ ይልሃል በለው፡፡ ፈርኦንም መልሶ እስራኤልን እለቅ ዘንድ እግዚአብሔር ማንው? በማለት የፈርዖን ልብ ደንድኖ አልሰማም አለ በዘጠኝ
መቅሰፍት በአስረኛው ሞተ በኩር ግብጻውያንን መታቸው እግዚአብሔርም ለሙሴ እንግዲህ አለው ጫማችሁን በእግራችሁ በትራችሁንም በእጃችሁ  አድርጋችሁ እንዲህ በሉት የእግዚአብሔር ፋሲጋ
ነው፡፡እኔም በዛች ሌሊት በግብጽ አገር ከሰው አስከ እንስሳ ድረስ በኩርን ሁሉ እገድላለሁ በግብጽ አማልክት ሁሉ እፈርድባች|ለሁ እኔ እግዚአብሔር ነኝ ደሙም ምልክት ይሆናች|ል፡፡(ዘጸ 11፡11)

እግዚአብሔርም ሙሴን #ሕዝቡን ከባርነት ከግብጽ የወጣችሁበትን ይህንን ቀን አስቡ; አለው፡፡(ዘጸ 13፡1) እንዲህም ሆነ እኩለ ሌሊት በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ከተቀመጠው ከፈርዖን በኩር ጀምሮ
በግዞት እስካሉት እስከ ምርኮኞች ድረስ የግብጻውያኑን በኩር መታ፡፡ህዝቡንም ነጻ አወጣ፡፡

v  ትምሕር
·         ሁሉን የሚያደርግ እግዚአብሔር በቻ መሆኑን ማወቅ
#እግዚአብሔር ስለ እናንተ ይዋጋል እናንተም ዝም ትለላችሁ;(ዘጸ 14፡14)
·         የነጻነት ቀን መዘከር
#ከባርነት የወጣችሁትን ይህን ቀን አስቡ;(ዘጸ 13፡1)
·         ድል ከእግዚአብሔር መሆኑን
#እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው; (ዘጸ 15፡3)
·         የግብጻውያን አማልክት የተዋረዱበት
·         የአግዚአብሔር አስደናቂ ተአምር የታየበት (ዘጸ 14፡14)
·         እስራኤላዊያን የተደሰቱበት (ዘጸ 15፡2)
v  መልእክት
ከ430 ዓመታት በ|ላ እስራኤላውያን ከፈርዖን  የባርነት አገዛዝ ወጥተዋል፡፡ እኛም በዘመናችን ከዲያብሎስ ባርነት መላቀቅ ይገባናል #በነፃነት ልንኖር ክርስቶስ ነጻ አውጥቶናልና; (ገላ 5፡1)
እኛም የማንረሳው ሌሊት ከሞት ውርደት የተነሣንበት ሌሊት ቃሉን በምስጋና ተሞልተን ስንዘምር ያደርንበትን ሌሊት ልንረሳው አይገባንም፡፡
                       የእግዚአብሔር ቸርነት አይለየን አሜን!!!