ረቡዕ 31 ዲሴምበር 2014

አስደናቂ የክርስቶስ ልደት



v  “በልዑል ዙፋን ላይ ተቀምጦ ያለ እርሱ በበረት ተጣለ፣ ስጋ ሳይሆን የነበረ የማይዳሰስ ወልድ ዋህድ ዘሬ ስጋን በመዋሃድ ተዳሰሰ፣ሃጥያትን ይቅር የሚል ራሱ በጨርቅ ተጠቀለለ” (ሃይማ.አበው ዘዮሐንስ አፈወርቅ)
v  “ኦ ለዝንቱ መንክር ልዑል…”ከህሊናት ሁሉ ለላቀ ለዚህ ድንቅ ምስጥር አድናቆት ይገባል፤ምድራዊት ሴት ሰው የሆነ እግዚአብሔር ቃልን ወለደችው፤ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤እርሱም እናቱን ፈጠረ፤ከእርሷም እርሱ የፈጠረውን ስጋ ተዋሐደ በእኛ ባህርይ ተወለደ እርሱም እኛን ስለመውደዱ ፈጠረን በእኛ ባህሪይ ወለደችው ፈጣሪም እንደሆነ ታወቀ፡፡(ቅ.ያዕቆብ ዘስሩግ)
v  “ዳያቢሎስ በልደት ማየት የተሳነውና ያስደነገጠው ብርሃን፤ዳግመኛም በዕለተ አርብ በብርሃን ነጸብራቅ ኃይል የጨለማውን አበጋዝ እውር ያደረገው ይህ ማን ነው፤ወገኖቼን እገዛ ዘንድ ያልተወኝ ይህ ማን ነው? ነገር ግን ተሰጠተውኝ የነበሩት ነፍሳትን ሁሉ ወደሰማይ ያወጣል እንጂ በማለት ፍጹም ሽንፈቱን ገልጾታል፡፡ ”(ትምህርተ ኅቡአትን ተመልከቱ)
v  #ዲያብሎስ በስጋ ከይሲ ተሰውሮ አዳምን ድል በነሳው ጌታ ድግሞ በጥበብ በስጋ ብእሲ ተሰውሮ ዲያብሎስን ድል ነስቶታል;(መቅድመ ወንጌል)
v  “ጌታ ሲወለድ በቤተልሔም ብርሃኑ ሲያበራ ሰይጣን እየተቻኮለ ከሰፈሩ በወጣ ጊዜ ክፉዉ ጭፍራ በጸጥታ ቆሞ ይጠብቀው ነበር፤ራሱም በርሮ ወጣ ወደ ከፍታዎችና ወደ ዝቅታዎችም ሁሉ ፈጠነ በሁሉም ክልሎችና ድንበሮች አለፈ፡፡ከሩቅ ሆኖ ወደ ቤተልሔም አቅጣጫ ተመለከተ አንድ መልኣክም በአስደናቂ ክብር የብርሃንንም ጸዳል ተላብሶ፤እየበረረ ሲዞር ሲመላለስም፤በደስታ ተመልቶ እና እየፈጠነ፤ውብ እና አስደሳች ሆኖ አሳቱ እጅግ እያበራ ከድምፁም ታላቅ ብርሃን እያመነጨ ሲያልፍ አየ፤ሰይጣንም አይቶት በፍርሃት እየራደ ተሸሸገ፡፡”(በቅዱስ ያእቆብ ዘስሩግ ድርሳን)
v  ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴ ማርያም ላይ “ትእምርተዋሕዱ ረሰየኪ አብ”አብ የራሱ ምልክት አደረገሽ አለ እርሱ ቅድመ ዓለም ያለ እናት፤አንድም ተቀዳሚ ተከታይ የሌለው የአንድ ልጅ ምልክት አደረገሽ አለ እሷ ድንግልወእም (ድንግልም እናትም) ስትባል መኖሯ ራሱም አምላክወ ሰብእ (አምላክም ሰውም) ሲባል የመኖሩ፤እርሷም ስትወልደው ማኀተመ ድንግልናዋ አለመለወጡ እርሱም ሰው ሲሆን ባህርየ መለኮቱ ያለመለወጡ ምሳሌነት በማለት ምሳሌነቱትን አስቀምጦል፡፡


ሰኞ 15 ዲሴምበር 2014

ታህሳስ 2007 ባታለማርያም በኮልፌ ደብረብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ

ታህሳስ 2007 ባታለማርያም በኮፌ ደብረብርሃን ቅድስት ላሴ ቤ/ክ

እግዚአብሔር አገልግሎታችን ይቀበልልን!!እንዲህ በደብረ ብርሃን እንዳማረብን ሰማያዊት በሆንችው ነጻ በምታወጣው በደብረ ጽዮን ይሰብሰበን!!!











ሐሙስ 11 ዲሴምበር 2014

“ስእለቴን ይዤ ወደ ቤትህ እገባለሁ” መዝ 65፡13

“ስእለቴን ይዤ ወደ ቤትህ እገባለሁ” መዝ 65፡13
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አባቷ ኢያቄም እናቷ ሐና ይባላሉ፡፡የተወለደችው በእግዚአብሔር ፈቃድ በብስራተ መልአክ ነው፡፡አባትና እናቷ እግዚአብሔርን ልጅ ብትሰጠን ብለው ተስለው ነበር ሦስት ዓመት ሲሆናት ኢያቄም ለሐና ይህች ልጅ አንድ ነገር ብትሆን ከእግዚአብሔር ከልጃችንም ሳንሆን እንዳንቀር ሆዷ ዘመድ ሳይወድ አፏ እህል ሳይለምድ ወስደን እንስጥ ብለው መባ ጨምረው ወደ ቤተመቅደስ ይዘዋት ሄዱ ሊቀ ካህኑ ዘካርያስ ይባላል ደወል መትቶ ሕዝቡን ሰብስቦ የምግቧ ነገርስ? አለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤል ኅብስት ሰማያዊ ጽዋዕ ሰማያዊ ይዞ ረቦ ታየ፡፡ዘካርያስም ለርሱ የመጣ መስሎት ከእርሱ ሊቀበል ተነሳ ወደ ሰማይም ራቀበት ከእርሱ ቀጥሎ ያለው ሊቀ ካህንም ሊቀበል ሲቀበርብ ራቀበት፡፡ካህናቱም ሕዝቡም በየተራ ቢቀርቡ ራቀባቸው ምን አልባት ለዚህች ብላቴና የመጣ እንደሆነ እንይ አሉ፡፡ሐናን ትተሻት እልፍ በይ አሏት፡፡ትታት እልፍ አለች ድክድክ እያለች እናቷን ስትከተል መልአኩ ፈጥኖ ወርዶ አንድ ክንፉን አንጥፎ አንድ ክንፉን ጋርዶ በሰው ቁመት ልክ ከመሬት ከፍ አድርጎ መግቧት ዐረገ፡፡ ለቀ ካህኑ ዘካርያስ የምግቧ ነገር ከተያዘ ብሎ ከመካነ ደናግል አስገብቶታል፡፡ኅብስተ ሰማያዊ ጽዋዐ ሰማያዊ እየተመገበች መላእክት እየጎበኞት አስራ ሁለት አመት በቤተመቅደስ ኖረች፡፡

1.   ትምህርት
·         ኢያቄምና ሐና ጸሎታቸውና ልመናቸው መሰማቱን “እግዚአብሔር የልመናዪን ድምጽ ሰምቶአልና ወደድኩት” (መዝ114፡1)
·         ስለትን ማክበር
“ተስለህ የማትፈጽም ብትሆን ባትሳል ይሻላል፡፡” (መክ5፡5)
2.   መልእክት

የሰው ልጆችን ልመና የማያስቀር አምላክ የኢያቄምንና የሐናን ጸሎት ሰምቶ የሰጣቸውን አንዲት ልጅ ነቢያት በብዙ ምሳሌ ትንቢት የተናገሩላትን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን በገቡት ቃል ኪዳን መሠረት ለልጃቸው ሳይሳሱ በሦስት ዓመቷ ወደ ቤተመቅደስ ይዘዋት ሄዱ፡፡እመቤታችን ቀድስት ድንግል ማርያም ሐርና ወርቅ እየፈተለች ሰማያዊ መና እየተመገበች በንጽሕናና በቅድስና ኖረ፡፡በዚህ ዘመን የምንኖር እኛም እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቅ ዘወትር ከመቅደሱ ሳንለይና በንጽሕናና በቅድስና እንድንኖር የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ጸሎት አይለየን አሜን፡፡